Pages

Tuesday, December 11, 2012

ብሉይ ኪዳን

2 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት

ብሉይ ኪዳን ማለት የቆየ፣ የጥንት ውል ወይም ስምምነት ማለት ነው፡፡ ከክርስቶስ ልደት በፊት ያለውን የአንድ አምላክ አማኞች የሆኑትን የዕብራውያንን ታሪክ ይተርዳል፡፡ በውስጡም ብዙ የተስፋ ቃሎችን የያዘ ነው፡፡ ስለ መሲሕ ክርስቶስ መምጣትም የተነገሩ ትንቢቶች በብዛት አሉበት፡፡ ኢሳ 7÷14

ብሉይ ኪዳን ከሐዲስ ኪዳን ተነጥሎ አይታይም፡፡ ምክንያቱም ብሉይ ኪዳን የሐዲስ ኪዳን ትንቢት ሲሆን ሐዲስ ኪዳን የብሉይ ኪዳን ፍጻሜ ነው፡፡ ሐዲስ ኪዳን በብሉይ ኪዳን ውስጥ አለ፡፡ ሆኖም ግን ነቢያት የተነበዩለት አምላክ ወልደ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘመኑንና ጊዜውን ቆጥሮ በተገለጠ ጊዜ ስውር የነበረው ሐዲስ ኪዳን ተገልጸል፡፡

የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከተጻፋት ጊዜ ፣ ከያዙት ሀሳብና ከአጻጻፋቸው ሁኔታ አንጻር በዐራት ምድቦች ይከፈላሉ፡፡ እነርሱም፡-

2.1 የሕግ መጻሕፍት

የሕግ መጻሕፍት የሚባሉት መጽሐፍ ኦሪትም በመባል ይታወቃል፡፡ ኦሪት ቃሉ የሱርስት ሲሆን ሕግ ማለት ነው፡፡ የሕግ መጻሕፍት በቁጥር አምስት ሲሆኑ የእነዚህ መጻሕፍት ጸሐፊም ሊቀ ነቢያት ሙሴ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት አምስቱ የሙሴ መጻሕፍትም ይበላሉ፡፡ እነዚህ መጻሕፍት እንደየይዞታቸው የተለያ ስያሜ ተሰጥቷቸዋል፡፡ ስያሜዎቻቸውና የየመጻሕፍቱ ይዘት እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡




1.     ኦሪት ዘፍጥረት /ዘልደት/

ይህ መጽሐፍ የሥነ-ፍጥረትን ልደት፣ አጀማመርና አመጣጥ የሚያስረዳ በመሆኑ ይህን ስያሜ አግኝቷል፡፡ ከሕግ መጻሕፍትም ሲጻፍ የመጀመሪያው ነው፡፡ ኦሪት ዘፍጥረት 50 ምእራፎች ያሉት ሲሆን የመጽሐፉም ይዘት እንደሚከተለው በአራት ዋና ዋና ክፍሎች በመክፈል ሙሉ ታሪኩንና ትምህርቱን ማጥናት ይቻላል፡፡ እነዚህም ክፍሎች የሚከተሉት ናቸው፡፡

2.     ኦሪት ዘጸአት
3.     ኦሪት ዘሌዋውያን
4.     ኦሪት ዘኁልቁ
5.     ኦሪት ዘዳግም
     

ምንጭ
  1. የመጽሐፍ ቅድስ ጥናት (ቁጥር 1) በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን በ/ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማሕበረ ቅዱሳን ፤ በመ/ር አባይነህ ቸሬ አበበ እና በዲ/ን ቴዎድሮስ በየነ
  2. የመጽሐፍ ቅድስ ጥናት ጥራዝ በመናገሻ ገ/ድ/ቅ/ጊ/ቤ/ክ/ሰ/ት/ቤት


Monday, February 13, 2012

የሳምንቱ ጥቅስ

__የዮሐንስ፡ራእይ፥ምዕራፍ፡13።______________
ምዕራፍ፡13፤
1፤አንድም፡አውሬ፡ከባሕር፡ሲወጣ፡አየኹ፤ዐሥር፡ቀንዶችና፡ሰባት፡ራሶች፡ነበሩት፥በቀንዶቹም፡ላይ፡ዐሥር፡ዘ ውዶች፡በራሶቹም፡ላይ፡የስድብ፡ስም፡ነበረ።
2፤ያየኹትም፡አውሬ፡ነብር፡ይመስል፡ነበር፥እግሮቹም፡እንደ፡ድብ፡እግሮች፥አፉም፡እንደ፡አንበሳ፡አፍ፡ነበሩ ።ዘንዶውም፡ኀይሉንና፡ዙፋኑን፡ትልቅም፡ሥልጣን፡ሰጠው።
3፤ከራሶቹም፡ለሞት፡እንደ፡ታረደ፡ኾኖ፡አንዱን፡አየኹ፥ለሞቱ፡የኾነውም፡ቍስል፡ተፈወሰ።ምድርም፡ዅሉ፡አውሬ ውን፡እየተከተለ፡ተደነቀ፥
4፤ለዘንዶውም፡ሰገዱለት፥ለአውሬው፡ሥልጣንን፡ሰጥቶታልና፤ለአውሬውም፦አውሬውን፡ማን፡ይመስለዋል፥ርሱንስ፡ ሊዋጋ፡ማን፡ይችላል፧እያሉ፡ሰገዱለት።
5፤ታላቅንም፡ነገርና፡ስድብን፡የሚናገርበት፡አፍ፡ተሰጠው፥ባርባ፡ኹለት፡ወርም፡እንዲሠራ፡ሥልጣን፡ተሰጠው።
6፤እግዚአብሔርንም፡ለመሳደብ፡ስሙንና፡ማደሪያውንም፡በሰማይም፡የሚያድሩትን፡ሊሳደብ፡አፉን፡ከፈተ።
7፤ቅዱሳንንም፡ይዋጋ፡ዘንድ፡ድልም፡ያደርጋቸው፡ዘንድ፡ተሰጠው፥በነገድና፡በወገንም፡በቋንቋም፡በሕዝብም፡ዅ ሉ፡ላይ፡ሥልጣን፡ተሰጠው።
8፤ከዓለምም፡ፍጥረት፡ዠምሮ፡በታረደው፡በግ፡ሕይወት፡መጽሐፍ፡ስሞቻቸው፡ያልተጻፉ፡በምድር፡የሚኖሩ፡ዅሉ፡ይ ሰግዱለታል።
9፤ዦሮ፡ያለው፡ቢኖር፡ይስማ።
10፤ይማረክ፡ዘንድ፡ያለው፡ማንም፡ቢኖር፡ወደ፡ምርኮነት፡ይኼዳል፤በሰይፍ፡የሚገድል፡ማንም፡ቢኖር፡ራሱ፡በሰ ይፍ፡እንዲገደል፡ይገ፟ባ፟ዋል።የቅዱሳን፡ትዕግሥትና፡እምነት፡በዚህ፡ነው።
11፤ሌላም፡አውሬ፡ከምድር፡ሲወጣ፡አየኹ፥የበግ፡ቀንዶችን፡የሚመስሉ፡ኹለት፡ቀንዶችም፡ነበሩት፡እንደ፡ዘንዶ ም፡ይናገር፡ነበር።
12፤በፊተኛውም፡አውሬ፡ሥልጣን፡በርሱ፡ፊት፡ዅሉን፡ያደርጋል።ለሞቱ፡የኾነውም፡ቍስል፡ተፈወሰለት፡ለፊተኛው ፡አውሬ፡ምድርና፡በርሱ፡የሚኖሩት፡እንዲሰግዱለት፡ያደርጋል።
13፤እሳትንም፡እንኳ፡ከሰማይ፡ወደ፡ምድር፡በሰው፡ፊት፡እስኪያወርድ፡ድረስ፡ታላላቆችን፡ምልክቶች፡ያደርጋል ።
14፤በአውሬውም፡ፊት፡ያደርግ፡ዘንድ፡ከተሰጡት፡ምልክቶች፡የተነሣ፡በምድር፡የሚኖሩትን፡ያስታል፤የሰይፍም፡ ቍስል፡ለነበረውና፡በሕይወት፡ለኖረው፡ለአውሬው፡ምስልን፡እንዲያደርጉ፡በምድር፡የሚኖሩትን፡ይናገራል።
15፤የአውሬው፡ምስል፡ሊናገር፡እንኳ፡ለአውሬውም፡ምስል፡የማይሰግዱለትን፡ዅሉ፡ሊያስገድላቸው፥ለአውሬው፡ም ስል፡ትንፋሽ፡እንዲሰጠው፡ተሰጠው።
16፤ታናናሾችና፡ታላላቆችም፡ባለጠጋዎችና፡ድኻዎችም፡ጌታዎችና፡ባሪያዎችም፡ዅሉ፡በቀኝ፡እጃቸው፡ወይም፡በግ ንባራቸው፡ምልክትን፡እንዲቀበሉ፥
17፤የአውሬውም፡ስም፡ወይም፡የስሙ፡ቍጥር፡ያለው፡ምልክት፡የሌለበት፡ማንም፡ሊገዛ፡ወይም፡ሊሸጥ፡እንዳይችል ፡ያደርጋል።ጥበብ፡በዚህ፡አለ።
18፤አእምሮ፡ያለው፡የአውሬውን፡ቍጥር፡ይቍጠረው፤ቍጥሩ፡የሰው፡ቍጥር፡ነውና፥ቍጥሩም፡ስድስት፡መቶ፡ስድሳ፡ ስድስት፡ነው።