Pages

Thursday, August 18, 2011

የሳምንቱ ጥቅስ

መዝሙር፡5
ለመዘምራን፡አለቃ፡በዋሽንት፤የዳዊት፡መዝሙር።
1፤አቤቱ፥ቃሌን፡አድምጥ፥ጩኸቴንም፡አስተውል፤
2፤የልመናዬን፡ቃል፡አድምጥ፥ንጉሤና፡አምላኬ፡ሆይ፥አቤቱ፥ወዳንተ፡እጸልያለኹና።
3፤በማለዳ፡ድምፄን፡ትሰማለኽ፥በማለዳ፡በፊትኽ፡እቆማለኹ፥እጠብቃለኹም።
4፤አንተ፡በደልን፡የማትወድ፟፡አምላክ፡ነኽና፤ክፉ፡ከአንተ፡ጋራ፡አያድርም።
5፤በከንቱ፡የሚመኩ፡በዐይኖችኽ፡ፊት፡አይኖሩም፤ክፉ፡አድራጊዎችን፡ዅሉ፡ጠላኽ።
6፤ሐሰትን፡የሚናገሩትን፡ታጠፋቸዋለኽ፤ደም፡አፍሳሹንና፡ሸንጋዩን፡ሰው፡እግዚአብሔር፡ይጸየፋል።
7፤እኔ፡ግን፡በምሕረትኽ፡ብዛት፡ወደ፡ቤትኽ፡እገባለኹ፤አንተን፡በመፍራት፡ወደ፡ቅድስናኽ፡መቅደስ፡እሰግዳለ ኹ።
8፤አቤቱ፥ስለ፡ጠላቶቼ፡በጽድቅኽ፡ምራኝ፤መንገዴን፡በፊትኽ፡አቅና።
9፤በአፋቸው፡እውነት፡የለምና፥ልባቸውም፡ከንቱ፡ነው፤ጕረሯቸው፡የተከፈተ፡መቃብር፡ነው፤በምላሳቸው፡ይሸነግ ላሉ።
10፤አቤቱ፥ፍረድባቸው፥በምክራቸውም፡ይውደቁ፤ስለ፡ክፋታቸውም፡ብዛት፡አሳዳ፟ቸው፥እነርሱ፡ዐምፀውብኻልና።
11፤ባንተ፡የሚታመኑት፡ዅሉ፡ግን፡ደስ፡ይላቸዋል፤ለዘለዓለሙ፡ደስ፡ይላቸዋል፥እነርሱንም፡ትጠብቃለኽ፤ስምኽ ንም፡የሚወዱ፡ዅሉ፡ባንተ፡ይመካሉ።
12፤አንተ፡ጻድቁን፡ትባርከዋለኽና፤አቤቱ፥እንደ፡ጋሻ፡በሞገስ፡ከለልኸን።

No comments:

Post a Comment